የጤና ሚኒስቴር በአለታ ወንዶ ከተማ በአነስተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ አባወራዎች ያስገነባቸው  ቤቶችን ለተጠቃሚዎች አስረከበ 

Aleta Wondo

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በክረምት በጎ አገልግሎት በአለታ ወንዶ ከተማ በዝቅተኛ ኑሮ ለሚገኙ ስድስት አባወራዎች/እማወራዎች ያስገነባቸውን ቤቶች ለተጠቃሚዎች ያስረከቡ ሲሆን በክረምት በጎ አገልግሎት የጤና ሚኒስቴር ችግኞችን የመትከል እና አቅመ ደካሞችን የማገዝ ስራን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው በአለታ ወንዶ ከተማም ምሳሌ መሆን የሚችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። ቤቶቹም መሰረታዊ መገልገያ ቁሳቁስ የተሟላላቸው ሲሆን ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። 


ድጋፍ የተደረገላቸው ግለሰቦችም በሰጡት አስተያየት መጠለያ ማጣት እጅግ አስቸጋሪ ህይወት እንዲመሩ እንደዳረጋቸው ሆኖም ጤና ሚኒስቴር  እንደደረሰላቸው እና ተስፋቸውን እንዳለመለመ ገልጸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 

አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን ወጪን በመጋራት  ወደ ስራ ለማስገባት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ይፋ የተደረገውን ፕሮጀክት አስመልክቶ ምክክር ተደርገ

HR

ጤና ተቋማት ያለባቸውን የሰው ሃይል እጥረት ለማቃለል እና ለተመራቂ ሃኪሞች የስራ እድል ለመፍጠር ይፋ የተደረገውን የ3 ዓመት ፕሮጀክት ስራ በተመለከተ ወርክሾፕ ተካሂደዋል።


ጤና ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች እና ክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በመሆን ወጪን  በመጋራት አዳዲስ ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት በተጀመረው ፕሮጀክት መሰረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት በጤና ሚኒስቴር የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ደምሴ በፕሮጀክቱ ከ2011 ጀምሮ ተመርቀው ያልተቀጠሩ 2898 ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል የበጀት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡

ትኩረት የሚሹ የሀሩራማ በሽታዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ በመቀናጀት መስራት ይገባል

NTD

በሲዳማ ክልል አስተናጋጅነት በሀገራችን ለሶስተኛ ጊዜ እየተዘከረ ባለው የአለም ትኩረት የሚሹ የሀሩራማ በሽታዎች ቀንን አስመልክቶ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ባስተላለፉት መልእክት እንደ ዝሆኔ/ፖዶኮኒዮሲስ፣ ሊንፋቲክ ፊላሪያሲስ፣ ሀይድሮ ሲል፣ ሌሽሚያሲስ የመሳሰሉ የቆላማ እና ሀሩራማ በሽታዎች ለረጅም ዘመን ትኩረት ሳያገኙ በመቆየታቸው ዜጎችን ለተለያዩ አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች እየዳረጉ መሆናቸውን ተናግረው ይህንን ለመቀየር ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን በሁሉም ስፍራ ማዳረስ ረገድ ሁሉም በጤና ዘርፍ እየሰሩ ያሉ አካላት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡ፣ እንዲሁም በጋራ በመቀናጀት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። 

የመሀል ሜዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መደበኛ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።" የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ 

Mehal Meda

በአሸባሪውና ዘራፊው ቡድን የሕክምና አገልግሎት ያቋረጠው የመሀል ሜዳ ሆስፒታል በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታልና በአካባቢው ማህበረሰብ በተደረገለት ድጋፍ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ ተናገሩ።


ሆስፒታሉ በተደረገለት የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችና የመድኃኒት አቅርቦት ድጋፍ የእናቶችና የህፃናት ጤና አገልግሎት፣ የድንተኛና ጽኑ ሕሙማን አገልግሎት የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በየእለቱ በአማካይ ከ 150 እስከ 200 ታካሚዎች አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጸው ሙሉ ለሙሉ ሆስፒታሉን ወደ ስራ ለመመለስ ተጨማሪ ድጋፎች እንደሚያስፈልጉ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።


በሆስፒተሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ አስካለ ገዛኸኝ እና አቶ በልዩ ካሳዬ ተመላላሽ ህክምና ክትትላቸው በመቋረጡ ከፍተኛ ስጋት እንዳሳደረባቸው ገልጸው ሆስፒታሉ አገልግሎት ጀምሮ በማየታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።

ጤና ሚኒስቴር ለአማራ ክልል ለወደሙ የጤና ተቋማት  አጋር አካላትን በማስተባበር ከ21 ሚሊየን ብር በላይ  የሚያወጡ የህክክምና ግብአቶችን፣ መድሀኒቶችን፣ አንቡላንሶችን እና የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አስረከበ። 

donation

የጤናማ እናትነት ወር በደሴ ከተማ በተከበረበት ስነስርአት ጤና ሚኒስቴር አጋር አካላትን በማስተባበር ለእናቶች እና ህጻናት ጤና ከፍተኛ እገዛ ማድረግ የሚችሉ ከ21 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ግብአቶችን፣ መድሀኒቶችን፣ ሁለት አንቡላንሶችን እና ጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አበርክቷል። 


የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት ወራሪው ሀይል ተቋሞቻችንን ቢያወድምም ጠንካራ መንፈሳችንን እና ህብረታችንን ከቶ ሊሰብር አይቻለውምና ከቀድሞ በበለጠ እጅ ለእጅ ያተያይዘን ተቋሞቻችንን እንገነባለን ሲሉ ተናግረዋል።

ደሴ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ወደ አገልግሎት አሰጣጥ በመመለሱ መደሰታቸውን ተገልጋዮች ገለፁ

Community

በጦርነቱ ምክንያት ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ የህክምና አገልግሎት መስጠት በጀመረው የደሴ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግልጋሎት በማግኘታቸው መደሰታቸውን ነዋሪዎች ገለፁ።


በሆስፒታሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ መሬሞ ሙሄ እና አቶ አበበ አብረሀም እንደገለፁት የሆስፒታሉ በሮች ተከፍተው ነጭ ገዋን የለበሱ የጤና ባለሙያዎች በፈገግታ ታካሚዎችን ሲያስተናግዱ በማየታቸው ተደስተዋል።


ህዳር 25/ 2014 ዓ ም በሆስፒታሉ እንድትገኝ ከሀኪሟ ቀጠሮ ተሰጥቷት እንደነበርና በነበረው ጦርነት ምክንያት እንዳላቀረበች የተናገራቸው መሬሞ ያ የስቃይ ጊዜ አልፎ ዛሬ ወደ ሆስፒታሉ በመቅረብ ተመርምራ መድሀኒት ሊታዘዝላት በመቻሉ ከጭንቀት እንደገላገላት መስክራለች።


እህቴን ለማሳከም መጥቼ ተገቢውን አገልግሎት አግኝቼ የራጅ ምርመራ ውጤት እየጠበቅን ነው ያለው አበበ በበኩሉ ለዚህ ብርሀናማ ቀን በመብቃታችን ፈጣሪንና መንግስትን አመሰግናለሁ ብሏል።

"የእናቶችን ሞት ለማስቀረት ሁሉም አካላት ቀዳሚ አጀንዳ በማድረግ ሊሰሩ ይገባል!" ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ

Dr. Dereje Duguma

"በማንኛውም ሁኔታ ከወሊድ በሁዋላ በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶች ሞት እጅ ለእጅ ተያይዘን እንግታ" በሚል መሪ ቃለ በአማራ ክልላዊ መንግስት ደሴ ከተማ በተከበረበት ወቅት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት በሀገራችን በቀን ከሰላሳ በላይ እናቶች ከወሊድ ጋር በተያያዘ ህይወታቸውን እንደሚያጡ ተናግረው እንደ ደሴ ባሉ በህውሀት አሸባሪ ቡድን የጦርነት ጥቃት እና ዘረፋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ችግሩ ሊከፋ እንደሚችል በመረዳት ሁሉም አካላት በከፍተኛ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡

 
አሸባሪው ብድን የጤና ተቋማቱን ቢያወድሙና ቢዘርፉም ጠንካራ መንፈሳችንን ግን ሊነኩት አይቻላቸውምና ደግመን ተረባርበን በመገንባት ለእናቶችና ለሌሎችም የጤና አገልግሎቶችን በተሻለ እናቀርባለን ብለዋል፡፡  

የኮቪድ 19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚያግዝ ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያ ድጋፍ ርክክብ ተደረገ

Delivery

ግምታቸው 30 ሚሊዮን ብር የሚሆን 100 ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያዎች የኮቪድ 19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚያግዝ ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያ ድጋፍ ለጤና ሚኒስቴር ተደርጓል፡፡

 
ድጋፉን ለጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ  ያስረከቡት የሞደርን ኢ.ቲ.ኤች አውት ሶርስ ፒ.ኤል.ሲ ተወካይ የሆኑት አቶ ታዲዮስ ተፈራ፤ ድጋፉ የተደረገው በኮቪድ የተጠቁ ዜጎችን ለመርዳት ታስቦ መሆኑን ገልጸው ድጋፋቸው የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

 
 የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ፣ ድጋፉን ያደረጉትን ድርጅቶች አመስግነው፤ መሳሪያዎቹ በጽኑ ህሙማን ማገገሚያ የሚገኙ ታካሚዎችን ለመርዳት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርጉ ገልጸው ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

"እናቶች በጤና ተቋማት በሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲወልዱ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት።"  ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

Dr. Dereje Duguma

የጤናማ እናትነት ወር "በማንኛውም ሁኔታ ከወሊድ በኋላ በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶችን ሞት እጅ ለእጅ ተያይዘን እንግታ" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ35ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ16ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስተባባሪነት በአበበች ጎበና የእናቶችና ህፃናት ሆስፒታል ተከብሯል፡፡ 


የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በዓሉን አስመልክተው ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ከእናቶች ሞት ጋር ተያይዞ በተደረገው ጥናት በዓመት ከሚሞቱት እናቶች በተለይ 50 በመቶ የሚሆኑት ከደም መፍሰስ ጋር በተያያዘ ምክንያት መሆኑን ገልፀው እናቶች በጤና ተቋማት በሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲወልዱ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል፡፡ ለዚህም የሃይማኖት አባቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የኪነጥበብ ሰዎች፣ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ በመፍጠር እናቶች በህክምና ተቋም እንዲወልዱ እንዲያበረታቱ አሳስበዋል፡፡

በጦርነት እና በተለያዩ ግጭቶች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና  ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል በጤና ሚኒስቴርና በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የተዘጋጀ የዘርፈ ብዙ ምላሽ እቅድ ይፋ ተደረገ

ministers

በተለያዩ ክልሎች በጦርነት እና በተፈጠሩ ግጭቶች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የተቀናጀ  የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና ምላሽ  በመስጠት እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ይበልጥ ለማጠናከርና ፈጣን ለማድረግ የጤና ሚኒስቴር እና የሴቶችና  ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር በጋራ ያዘጋጁት እቅድ ለባለድርሻ አካላት በኢትዮጵያ የህረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች የመልሶ ማቋቋምና ሪዚሊየንስ ዳይሬክተር በሆኑት በዶ/ር ያረጋል ፉፋ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።


በቅንጅታዊ  ርብርቡ የስነ አዕምሮ ፣  የስነ ልቦና እና የማህበራዊ ስራዎች እንዲሁም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ የመፍጠር ተግባራት እንደሚከናወኑ በእቅዱ የተካተቱ ዝርዝር አላማዎች ያሳያሉ፡፡