Articles

በጦርነቱ ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች በተደረገ ከሀያ አራት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የአይን ሕክምና ድጋፍ ከሶስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የአይን ቀዶ ጥገና ህክምና መስጠት መቻሉ ተገለጸ፡፡

የአይን ሞራ ግርዶሽ  የነጻ ህክምና

የጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት በአይን ህክምና ዙሪያ ከሚሰሩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር ከሃያ አራት ሚሊየን ብር በላይ  ድጋፍ በማሰባሰብና የህክምና ባለሙያቸው ድጋፍን በማቀናጀት በአፋር እና በአማራ ክልሎች  በጦርነቱ ምክንያት ህክምና ሳያገኙ የቆዩ ከሶስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የአይን ሞራ ግርዶሽ  የነጻ ህክምና መስጠት መቻሉን  እና የህክምና ተቋማቱም በመደበኛ አገልግሎታቸው ህክምናውን መስጠት የሚያስችላቸው ስራ መከናወኑን  የጤና ሚኒስትር የበሽታ መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሕይወት ሰሎሞን  አስታወቁ፡፡

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተለያዩ  አገልግሎቶች ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ

Inauguration

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት ጥራት ያለው ህክምና ተደራሽነትን ለማሻሻልና  የስፔሻሊቲ እና ሰብ ስፔሻሊቲ ህክምና አገልግሎትን ለመስጠት የተለያዬ የህክምና ቴክኖሎጅዎችን መጠቀም እንደሚያስፈልግ ገልፀው በዛሬው እለትም በዋቻሞ ዩንቨርስቲ የንግስት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበት የተተከለ የሲቲ ስካን ማሽን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


በተጨማሪም በሆስፒታሉ ለሚገነቡት የኦክስጅን ማምረቻና 450 አልጋ የሚይዝ የእናቶችና ህፃናት ጤና አገልግሎት መስጫ ማዕከል የመሰረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል።


የዋና ዋና ከተሞች የድንገተኛ፤ አደጋና ጽኑ ህክምና አገልገሎት ማሻሻያ ፕሮግራም (Major city Emergency and Critical services Improvement Program(MECIP) በተመለከተም የቅድመ ጤና ተቋም የጥሪ ማዕከል አገልግሎትን አስጀምረዋል።

ኢትዮጵያ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎቿን የኮቪድ-19 በሽታ መከላከያ ክትባት እንዲከተቡ አድርጋለች!

Dr. Tegene Regassa

የ2ኛ ዙር የኮቪድ-19 ክትባት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫውን የሰጡት የጤና ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ዶ/ር ተገኔ ረጋሳ ሁለተኛ ዙር የኮቪድ 19 ክትባት ዘመቻ በአገር አቀፍ ደረጃ ከየካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን በአሁኑ ዘመቻ የተሰጠውን ከ14 ሚሊዮን በላይ ክትባትን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መከተብ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡


እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነ 17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሙሉ ለሙሉ ክትባት የወሰዱ ሲሆን ከአንድ መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ በላይ የሚሆኑት የማጠናከርያ ክትባቱን (Booster dose) ተከትበዋል፡፡ በጥቅሉ ከ25 ሚሊዮን በላይ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውልም ተደርጓል፡፡  


በዘመቻውም በመጀመርያው ዙር የመከላከያ ክትባቱ ያልተሰጠባቸው የአማራ እና የአፋር ክልሎችን በማካተት ክትባቱን መስጠት መቻሉንም ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል፡፡