Articles

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ምግብን መሠረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ ይፋ ተደረገ 

Nutrition

የጤና ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር እና አጋር አካላት በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስተባባሪነት በጋራ ያዘጋጁት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ምግብን መሠረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ (Food-Based Dietary Guidelines (FBDG's) በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል። 

‘የጤና መረጃ ሥርዓትን ለማሻሻል አጋርነት እና ትብብርን ማጠናከር’ በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የጤና መረጃ ሳምንት ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከበረ ነው።

DATA WEEK

በበዓሉ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትር ፅ/ቤት ሀላፊ ዶ/ር ሩት ንጋቱ በጤናው ሴክቴር የሚታየውን የመረጃ ጥራት ተደራሽነት እና አጠቃቀም ጉድለት በመቅረፍ የጤና አግልግሎት ዘርፉን ማሻሻል እና ተደራሽ ማድረግ ዋና የትኩረት አቅጣጫው መሆኑንን ገልፀው የጤናው ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የትግበራ ዘመን የጤና መረጃ ጥራትን ለማሻሻል የመረጃ አጠቃቀም ባህሪን ለማጎልበት እና መረጃን ዋቢ ያደረገ የውሳኔ አስጣጥ አስራርን ለማስረፅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በጦርነቱ ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች በተደረገ ከሀያ አራት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የአይን ሕክምና ድጋፍ ከሶስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የአይን ቀዶ ጥገና ህክምና መስጠት መቻሉ ተገለጸ፡፡

የአይን ሞራ ግርዶሽ  የነጻ ህክምና

የጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት በአይን ህክምና ዙሪያ ከሚሰሩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር ከሃያ አራት ሚሊየን ብር በላይ  ድጋፍ በማሰባሰብና የህክምና ባለሙያቸው ድጋፍን በማቀናጀት በአፋር እና በአማራ ክልሎች  በጦርነቱ ምክንያት ህክምና ሳያገኙ የቆዩ ከሶስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የአይን ሞራ ግርዶሽ  የነጻ ህክምና መስጠት መቻሉን  እና የህክምና ተቋማቱም በመደበኛ አገልግሎታቸው ህክምናውን መስጠት የሚያስችላቸው ስራ መከናወኑን  የጤና ሚኒስትር የበሽታ መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሕይወት ሰሎሞን  አስታወቁ፡፡