Articles

የእናቶችና የህፃናት ጤናን ለማሻሻል የሚያግዙ 10 ተንቀሳቃሽ የህክምና ክሊኒኮችን ለመለገስ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ፡፡

mobile medical

የጃፓን መንግስት በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎትን ፍትሃዊና ተደራሽን ለማጠናከር የሚያግዙ የተሟላ የህክምና ቁሳቁስ ያላቸው 10 ተንቀሳቃሽ የህክምና ክሊኒኮችን ለመለገስ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል

በጃፓን መንግስት በኩል ስምምነቱን የፈረሙት በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታኮኮ ባስተላለፉት መልዕክት በሀገራቸው የተደረገው የ500 ሚሊዮን የጃፓን የን/3.5 ሚሊዮን ዶላር/ ድጋፍ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ክልሎች ድጋፍ የሚሹ ተብለው በተለዩት በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላና በደቡብ ምዕራብ ክልሎች ያለውን የእናቶችና ህፃናት ጤና በማሻሻል የሚሞቱ እናቶችና ህፃናትን ቁጥር እንደሚቀንስ ያላቸውን ተስፋ ጠቁመው ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮቹ አልትራሳውንድና ኤሌክትሮ ካርዲዮግራፍን ጨምሮ መሰረታዊ የህክምና ቁሳቁሶችን ያሟሉ እንደሚሆኑ ገልፀዋል፡፡

ጤና ሚኒስቴር በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ከረዩ ሰፈር ሶስት የአቅመ ደካማ ቤቶችን ሰርቶ አስረከበ።

handed over three houses

ጤና ሚኒስቴር በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ከቤት እድሳት በተጨማሪ የአረንጓዴ ልማትና የአካባቢ ጥበቃ፣ የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ፣ ነፃ የህክምና አገልግሎት፣ የደም ልገሳና ማዕድ ማጋራት ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሌሎችም ክልሎች ማከናወኑን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰን በመወከል አቶ እስክንድር ላቀው የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተናግረዋል።


በዘንድሮው ዓመት የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ጤና ሚኒሰቴር ሰፋፊ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን በተለይም ድጋፍ የሚሹ ቤተሰቦች ቤቶችን ከማደስ ጋር ተያይዞ ከአዲስ አበባ ከተማ በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማም የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በእለቱም ቤት ለታደሰላቸው አቅመ ደካማ ግለሰቦች የቁልፍ ርክክብ አድርገዋል።

የስርዓተ ምግብ ትግበራን ለማጠናከር የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የጋራ የምክክር መድረክ ተካሄደ

Dr. Lia Tadesse

በሰቆጣ ቃልኪዳን የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን ለሌሎች የአፍሪካ ሃገራት በማጋራት በአፍሪካ ደረጃ መቀንጨርን ለማስቀረት፣ የሰው ሀብትን ለማሳደግ፣ እና በዘርፉ እድገትን ለማፋጠን አላማ አድርጎ በኢትዮጵያ መንግስት እና በአፍሪካ ልማት ባንክ ትብብር የተባበሩት መንግስታት አጠቃላይ ጉባኤ እየተካሄደ ባለበት በአሜርካ ኒዉዮርክ ከተማ የተዘጋጀ የጎንዮሽ መድረክ ነው።


በመድረኩ ላይ ኢትዮጵያ የመቀንጨር ምጣኔን ከመቀነስ አኳያ እየሰራች ያለውን ዘርፍ ብዙ ትብብርና ምላሽ አጠቃላይ ልምድና በሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነት የተገኙ መልካም ተሞክሮ በኢፌድሪ  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በክቡር አቶ ደመቀ መኮንን ቀርበዋል።