Articles

የባዮ ሜዲካል ኢንጅነሮችና ቴክኖሎጅስቶች በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህክምና መሳሪያዎችን መጠገን ጀመሩ

news

በክረምት የሚሰጠው የበጎ ፈቃድ የጤና አገልግሎት አንድ አካል የሆነው የባዮ ሜዲካል ኢንጅነሮችና ቴክኖሎጅስቶች የህክምና መሳሪያዎች ጥገና ስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም የጤና ሚኒስትሮች፣የጳውሎስ ሆስፒታል ዋና ፕሮቮስትና የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች፣ አስመጭና አምራች ድርጅቶች በተገኙበት በጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ተካሂዷል፡፡


የጤና አገልግሎት ህይወት የሚሰጥበት የበጎ ፈቃድ አገልገሎት መሆኑን የጠቀሱት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ከሚገኙ ነጻ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት በተጨማሪ የባዩ ሜዲካል ኢንጅነሮችና ቴክኖሎጅስቶች ወደ በጎ ስራ አገልግሎቱ መግባታቸው ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርና በሁሉም ዘርፎች ሀገርን ዝቅ ብሎ ማገልገል ክብር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የህክምና አገልግሎት መስጫ መሳርያዎች ማደሻና ማሻሻያ ማዕከል ግንባታ መጀመር የሚያስችል የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

Dr. Mekdes Daba

ጤና ሚኒስቴር ከኮሪያው ሪፐብሊክ ዓለም አቀፍ የጤና እንክብካቤ ፋውንዴሽን (ኮፊ) ጋር በመተባበር የህክምና አገልግሎት መስጫ መሳርያዎች ማደሻና ማሻሻያ ማዕከል ግንባታ መጀመር የሚያስችል የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።


በግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ የቆየ ወዳጅነት ያላቸው፣ በክፉና ደግ ጊዜያትም በአብሮነታቸው የጸኑ ሀገራት ናቸው ያሉት ዶ/ር መቅደስ ይህንን ሃገራዊ የህክምና መገልገያ እቃዎች ማደሻና ማሻሻያ ማዕከል ከደቡብ ኮሪያ መንግስት ጋር ስንጀምረው በተያዘለት ጊዜ እንደሚጠናቀቅ ከመተማመናችንም በላይ የሁለቱን ሀገራት ወዳጅነት እና ትስስር የበለጠ እያጠናከርንም ጭምር ነው ብለዋል።

"ጤናን ጨምሮ የዜጎቻችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የምናረጋግጠው በመደጋገፍ እሳቤ ነው" አቶ አሻድሊ ሀሰን - የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር

news

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጤናው ዘርፍ የክረምት የበጎ ፍቃድ ስራዎች ማስጀመርያ መርሀ ግብር ተካሄዷል። በዚህም የቤት እድሳት፣ የተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ፣የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሮች ተካሂደዋል ።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻዲሊ ሀሰን እንደተናገሩት በክልሉ በሚደረጉ ዘርፈ ብዙ የልማት እንቅስቅሳሴዎች ውስጥ ጤና ዋነኛው መሆኑን ጠቁመው የክልሉን ማህበረሰብም የጤና አገልግሎት ለማሻሻል እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰሩ ላሉት ተግባራት ጤና ሚኒስቴር እያደረገ ላለው ድጋፍ በክልሉ መንግስትና ህዝብ አመስግነዋል።

ጤናን ጨምሮ የዜጎቻችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የምናረጋግጠው በመደጋገፍ እሳቤ እና በጋራ ተቀናጅተን መስራት ስንችል ነው ብለዋል ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አሻድሊ ሀሰን።