በኢንዶኔዢያ ጃካርታ በውሃ፣ በሳኒቴሽን እና በሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከ37 ሀገራት የተውጣጡ የዘርፉ ሚኒስትሮች የልምድ ልውውጥ እና ውይይት እያካሄዱ ነው
በመድረኩ በዓለም መንግስታት የሚደገፍ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ሲቪክ ማህበራት፣ የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች፣ የልማት ባንኮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ውይይቱ በዘላቂ የልማት ግብ 6 ማለትም ዘላቂ የመሰረታዊ ውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገሌግሎት ለሁሉም ማዳረስ ላይ ያጠነጠነ ነው።
በጃካርታ እየተካሄደ ያለው መድረክ በዋነኝነት በ2030 እ.ኤ.አ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገልግሎቶችን ግብ ለማሳካት ወሳኝ በሆኑት የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ተጨማሪ ኢንቨስትመንት፣ አመራር እና ተጠያቂነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።
በሁለት ቀናት ቆይታው ከውሃ፣ ከሳኒቴሽን እና ከሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች በተጨማሪ የጎንዮሽ ውይይቶች በዘርፉ ሚኒስትሮች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡