የፋይናንስ እና ግዥ ዳይሬክቶሬት
ከመንግስትም ሆነ ከልማት አጋሮች የተገኙ የገንዘብ ሀብቶች ተገቢ አጠቃቀምን ማረጋገጥ!
የዳይሬክቶሬቱ ዓላማ
የፋይናንስና ግዥ ዳይሬክቶሬት ዓላማ ከመንግስትም ሆነ ከልማት አጋሮች የተገኙ የፋይናንስ ሀብቶች ተገቢ አጠቃቀምን ከማረጋገጥ በተጨማሪ የሚኒስቴሩ የገንዘብ ገቢና ወጪዎች በሀገሪቱ የፋይናንስ ሕጎችና መመሪያዎች መሠረት መከናወናቸውን እንዲሁም የጤና ልማት አጋሮች መስፈርቶችን ማክበራቸውን ማረጋገጥ ነው። በተጨማሪም የእርዳታ ፈንድ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ለታለመበት ዓላማ መዋሉን ማረጋገጥ እንዲሁም በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሪፖርት ማድረግ፣ ለጤናው ዘርፍ ስኬት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ዕቃዎችና አገልግሎቶችን አቅርቦትና አስተዳደርን ማመቻቸት የዳይሬክቶሬቱ ዓላማ ነው።