የቤተሠብ እቅድ አገልግሎትን ለማስፋፋት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የድርሻቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ ገለፁ።
ይህ የተገለፀው የጤና ሚኒስቴር በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት ተደራሽነት፣ ስኬት እና ክፍተት በተመለከተ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረገው የግንዛቤ መስጨበጫ መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ እንዳሉት የቤተሠብ እቅድ አገልግሎት መስጠት የሴቶች እና ህጻናት ህይወት ለመታደግ ዋነኛው አቅጣጫ መሆኑን ጥናቶች እንደሚያመለክቱ ጠቅሰው ይህን አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረት ተሠጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ ገልጸዋል።
ባለፉት አመታት በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት የተሠሩ ሥራዎች እና የተገኙ መሻሻሎች እንደተጠበቁ ሆነው አሁንም 22 በመቶ የሚሆኑ በለትዳር ሴቶች አገልግሎቱን ለማግኘት ቢፈልጉም ተደራሽ ማድረግ አለመቻሉን የገለጹት ሚኒስትር ድኤታው ይህም በበጀት አመቱ የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት መሆኑም አስረድተዋል።
- Read more about የቤተሠብ እቅድ አገልግሎትን ለማስፋፋት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የድርሻቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ ገለፁ።
- Log in or register to post comments
- 60 views