Articles

የቤተሠብ እቅድ አገልግሎትን ለማስፋፋት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የድርሻቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ ገለፁ። 

House of Representatives

ይህ የተገለፀው የጤና ሚኒስቴር በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት ተደራሽነት፣ ስኬት እና ክፍተት በተመለከተ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረገው የግንዛቤ መስጨበጫ መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ እንዳሉት የቤተሠብ እቅድ አገልግሎት መስጠት የሴቶች እና ህጻናት ህይወት ለመታደግ ዋነኛው አቅጣጫ መሆኑን ጥናቶች እንደሚያመለክቱ ጠቅሰው ይህን አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረት ተሠጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ ገልጸዋል።


ባለፉት አመታት በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት የተሠሩ ሥራዎች እና የተገኙ መሻሻሎች እንደተጠበቁ ሆነው አሁንም 22 በመቶ የሚሆኑ በለትዳር ሴቶች አገልግሎቱን ለማግኘት ቢፈልጉም ተደራሽ ማድረግ አለመቻሉን የገለጹት ሚኒስትር ድኤታው ይህም በበጀት አመቱ የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት መሆኑም አስረድተዋል።

የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነት ከደረሰበት ጉዳት አገግሞ ሁሉንም አገልግሎቶች በመስጠት ላይ ነው::

Boru Meda General Hospital

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ የሆስፒታሉን የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት ሆስፒታሉ ከደረሱበት ችግሮች ፈጥኖ በማገገም ለተገልጋዮች የተሟላ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የሚደነቅ ነው ብለዋል።


የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነቱ ወቅት ከፍተኛ ውድመት ከደረሰባቸው ሆስፒታሎች አንዱ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር አየለ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ የተረባረቡትን ሁሉ አመስግነው በቀጣይም የጤና ሚኒስቴር የጎደሉ የህክምና መሳሪያዎችን ለማሟላት እየተፈፀሙ ያሉ ግዢዎችን በማፋጠን ሆስፒታሉ የሚጠናከርባቸውን አማራጮች ሁሉ እንደሚያመቻች ተናግረዋል።

የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ለጤና ሚኒስቴር የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ጤናን ለማሻሻል የሚረዳ የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ::

Dr. Lia Tadesse

የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ለጤና ሚኒስቴር 31,076,584 ብር የሚያወጣ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ,በቤንሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ጤናን ለማሻሻል በዩኒሴፍ አመቻችነት የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ባደረገው  የገንዘብ ድጋፍ የህክምና መሳሪያዎች እና ለትራንስፖረት አገልግሎት የሚውሉ ሞተር ሳይክሎችን ለጤና ሚኒስትር አስረክቧል፡፡