Articles

ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብን መፍጠር ለሰላም መረጋገጥ የሚኖረው ድርሻ ከፍተኛ ነው።

75th Annual World Health Summit

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በስዊዘርላንድ ጀኔቫ "ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው 75ኛው አመታዊ የአለም  ጤና ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብን መፍጠር መቻል አስተማማኝና ዘለቄታዊ ያለው ሰላም እንዲኖር ከማድረግ አንጻር ያላው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።


ያለሰላም የተሟላ ጤናም መኖር አይችልም ያሉት ሚኒስትሯ  በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት በርካታ የጤና ተቋማት እንደወደሙና እንደተዘረፉ በዚህም በርካታ ቁጥር ያለው ህብረተሰብ የተሟላ የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ መስተጓጓሉን ጠቅሰው የኢትዮጵያ መንግስት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የጤና አገልግሎትን ወደነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ የሚመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ነው።

World Health Assembly

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ በአካል የመጀመሪያ የሆነው ይህ የጤና ጉባኤ ግንቦት 14, 2014 ዓ.ም  በጄኔቫ ዝዊዘርላንድ በይፋ ተጀምሯል። 


"ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!"( "Peace for Health and Health for peace!") በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው 75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ የአለማችን የማህበረሰብ ጤና  አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ሲሆን ጉባኤው ለአንድ ሳምንት በጄኔቫ የሚቀጥል ይሆናል።

በኢንዶኔዢያ ጃካርታ በውሃ፣ በሳኒቴሽን እና በሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከ37 ሀገራት የተውጣጡ የዘርፉ ሚኒስትሮች የልምድ ልውውጥ እና ውይይት እያካሄዱ ነው

 በውሃ፣ በሳኒቴሽን እና በሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከ37 ሀገራት የተውጣጡ የዘርፉ ሚኒስትሮች የልምድ ልውውጥ እና ውይይት

በመድረኩ በዓለም መንግስታት የሚደገፍ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ሲቪክ ማህበራት፣ የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች፣ የልማት ባንኮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ውይይቱ በዘላቂ የልማት ግብ 6 ማለትም ዘላቂ የመሰረታዊ ውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገሌግሎት ለሁሉም ማዳረስ ላይ ያጠነጠነ ነው።

በጃካርታ እየተካሄደ ያለው መድረክ በዋነኝነት በ2030 እ.ኤ.አ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገልግሎቶችን ግብ ለማሳካት ወሳኝ በሆኑት የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ተጨማሪ ኢንቨስትመንት፣ አመራር እና ተጠያቂነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።

በሁለት ቀናት ቆይታው ከውሃ፣ ከሳኒቴሽን እና ከሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች በተጨማሪ የጎንዮሽ ውይይቶች በዘርፉ ሚኒስትሮች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡