Articles

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የአከርካሪ ቀዶ ህክምና ማዕከል /National spine center/ ስራ ጀመረ 

St. Paul

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ግቢ የተገነባዉ የአከርካሪ ቀዶ ህክምና ማዕከል /National spine center/ የጤና ሚኒስትር እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ በኢትዮጵያ የእስራኤል ም/አምባሳደር፣ የጄዲሲ መስራችና አንጋፋ የቀዶ ህክምና ባለሙያዎች የቅዱስ ጳውሎስ አመራሮች እንዲሁም በርካታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተመርቆ ስራ ጀምሯል።

የጤና ሚኒስቴር የህብረተስብ ጤና አደጋዎችና በሽታዎች አስቀድሞ መከላከልና መቆጣጠር ላይ ከአሜሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር (CDC) ጋር የትብብር ስራውን አጠናክሮ መቀጠል በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ ዉይይት አድርገዋል

CDC

በውይይቱ ወቅት፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከCDC ጋር ለረጅም ጊዜ የተገነባው ትብብር በጤና ስርአት ማጠናከር፣ በኤች አይ ቪ ኤድስና በወባ ፕሮግራሞች እንዲሁም በላብራቶሪ አቅም ግንባታ ዘርፍ ያስመዘገበውን ግልጽ ውጤት በማስታወስ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።


በቀጣይም ይህ ትብብር በተለይ በድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነት እና ምላሽ አሰጣጥ ስርዓትን ማጠናከር እንዲሁም በክትባት አገልግሎት እና በመረጃ ስርዓት ማዘመን ዘርፎች ላይ በይበልጥ እንዲጠናከር ጠይቀዋል። 


የግሎባል ሄልዝ ሴንተር ሪጂናል ዳይሬክተር ማርታ አከርስ በበኩላቸው የአሜሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር (CDC) የኢትዮጵያ የጤና ስርአትን ለማጠናከር መስራቱን እንደሚቀጥል በመግለፅ፣ የጤና ሚኒስትር የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በተለይ በበለጠ ቅርበት አብረው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከካርተር ማዕከል ተወካዮች ጋር በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ የጋራ ጥረቶችን ለማጠናከር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል

Minister

በስብሰባው ወቅት ሁለቱም ወገኖች በጤና ሚኒስቴር እና በድርጅቱ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ገምግመዋል፡፡ በተለይም በበሽታ መከላከል፣ ክትትል እና ማጥፋት ፕሮግራም ዘርፎች፣ ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን፣ የጊኒ ወርም በሽታን እና ሌሎች ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የጤና ጉዳዮች ጨምሮ ለተገኘው እድገት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።


ዶ/ር መቅደስ የካርተር ማዕከል እያደረገ ለሚገኘው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድናቆታቸውን ገልጸው፤ ማእከሉ በመላ አገሪቱ የጤና ውጤቶችን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በቅርበት ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት ያስታወቁ ሲሆን፤ ጥራት ያላቸውን አገልግሎቶች ተደራሽነት ለማስፋት በትብብር መስራታቸውን እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።