የባዮ ሜዲካል ኢንጅነሮችና ቴክኖሎጅስቶች በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህክምና መሳሪያዎችን መጠገን ጀመሩ
በክረምት የሚሰጠው የበጎ ፈቃድ የጤና አገልግሎት አንድ አካል የሆነው የባዮ ሜዲካል ኢንጅነሮችና ቴክኖሎጅስቶች የህክምና መሳሪያዎች ጥገና ስራ ማስጀመሪያ ፕሮግራም የጤና ሚኒስትሮች፣የጳውሎስ ሆስፒታል ዋና ፕሮቮስትና የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች፣ አስመጭና አምራች ድርጅቶች በተገኙበት በጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ተካሂዷል፡፡
የጤና አገልግሎት ህይወት የሚሰጥበት የበጎ ፈቃድ አገልገሎት መሆኑን የጠቀሱት የጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰሩ ከሚገኙ ነጻ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት በተጨማሪ የባዩ ሜዲካል ኢንጅነሮችና ቴክኖሎጅስቶች ወደ በጎ ስራ አገልግሎቱ መግባታቸው ተጨማሪ አቅም እንደሚፈጥርና በሁሉም ዘርፎች ሀገርን ዝቅ ብሎ ማገልገል ክብር መሆኑን ገልጸዋል፡፡