Articles

ኢትዮጵያ እንደ ዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች - የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ 

WHA79

በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በ79 ነኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ገብቷል።


ዶ/ር መቅደስ ለልዑካን ቡድኑ ኦሪየንቴሽን በሰጡት መድረክ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለይም እንደ የዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች ብለዋል። 


ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት አባል ሀገር እንደመሆኗ በጉባኤዉ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና ቀጣይ ስራዎች የራሷን ድርሻ እንደምትወጣ ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።


ወቅታዊ የኢቦላና ሀንታ ቫይረስ ሁኔታን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ስጋት የሆኑ ወርሽኞችን መከላከልና መቆጣጠር በዋናነት በጉባኤዉ ቀርበዉ ዉይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።

የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን ኃላፊነት አስመልክቶ የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ዉጤታማ  ውይይት አድርገዋል 

AI

በውይይታቸዉም በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን፤ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረዋል።


የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት ናቸዉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። 

የአውሮፓ - የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካ ጤና አጋርነት ከ100 ሚሊዮን ዩሮ በላይ የድጋፍ ፓኬጆች ይፋ ሆኑ

EU-African Union

የአፍሪካን የጤና ደኅንነት፣ ጽናትና ሉዓላዊነት በማጠናከር ረገድ ትልቅ ምዕራፍ የሆነውን የአፍሪካ-አውሮፓ ህብረት የጤና አጋርነት የድጋፍ ፓኬጆች በሶስት አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።

ጠንካራ ስርዓት፣ ጠንካራ ተቋማት እና ለማህበረሰቡ የተሻሉ የጤና ውጤቶች እንዲመጡ ከአፍሪካ ሲዲሲ፣ ከአውሮፓ ህብረት እና ከሁሉም አጋሮች ጋር በቅርበት ለመስራት ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነች ብለዋል የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ።

ሁለቱ አህጉራት የአፍሪካን የጤና ሉዓላዊነት እና ሰፊ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወቅታዊና የወደፊት የጤና ስጋቶችን ለመቅረፍ እየተደረገ ያለውን ጥረት በመቀጠል የአፍሪካ - የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማእከል ሲዲሲ የረጅም ጊዜ እና አጠቃላይ የጤና አጋርነታቸውን አጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቁመዋል።