Articles

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመቆጣጠር ረገድ ስኬታማ ሆናለች 

Dr Mekdes Daba

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስን በመቆጣጠር ያደረገችው ስኬታማ ጥረት በጠንካራ አመራር፣ ፈጣን ምላሽ እና በተቀናጀ እርምጃ ትልቅ የህብረተሰብ ጤና ስኬትን ማስመዝገቧን የኤፌዴሪ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ታገሰ ጫፎ ገልፀው፤ ስኬቱ የጤና ፖሊሲ፣ የጤና ባለሙያዎች፣ እና ባለድርሻ አካላት የጋራ የመተባበር እና የመደመር ውጤት ነው ብለዋል።
 
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ  በሃገራችን የጤና ታሪክ ትልቅ የስኬት አሻራ የጣለ ተሞክሮ መሆኑን ገልፀው፤ ማህበረሰቡን በማስተባበር ፈጣን ምላሽ በመስጠት ቫይረሱ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት መቀነስ መቻሉን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ በአዲስ ቴክኖሎጂ ህክምና የሚሰጥ የመጀመሪያው የስትሮክ ህክምና ማእከል በዛሬው እለት ተመርቆ ተከፍቷል።

stroke treatment center

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሠ በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንዳሉት የጤናው ዘርፍ በርካታ መሻሻሎች እያሣየ ያለ ቢሆንም ገና ብዙ ወደ ፊት መሄድ ይጠበቅበታል ብለዋል። የአክሶል ስትሮክ እና ስፓይን ማእከል መከፈቱ እንደ ሀገር የእስትሮክ ህክምናን አንድ ምእራፍ ወደ ፊት የሚወስድ መሆኑን ጠቅሰው ማእከሉ  ለዚህ ምረቃ በመድረሱ ያላቸውን አድንናቆት ገልጸዋል። ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ እና የተለየ አገልግሎት ይዞ የመጣ ማእከል በአገሪቱ መከፈት መቻሉ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ዶክተር ሊያ ተናግረዋል።


ላለፋት አመታት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና በዚህ ሳቢያ የሚመጣ ሞት እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ዶክተር ሊያ ይህን ችግር ለመቅረፍ የጤና ሚኒስቴር ከመከላከል ስራው ጎን ለጎን የስፔሻሊቲ ህክምና አገልገግሎት ማስፋፋት ስራ የሚያሰራ የአስር አመት ፍኖተ ካርታ  ተዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን አስረድተዋል።

የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ተጀመረ

Breast cancer

በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ በፈረንጆች ጥቅምት ወር የሚደረገው የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ በፓዮኒር ምርመራ ማዕከል ከመስከረም 20 ጀምሮ ለአንድ ወር በነፃና በግማሽ ክፍያ በሚሰጥ ምርመራ ተጀምሯል።


በየዓመቱ 40 ሺህ ያህል ሰዎች በጡት ካንሰር ምክንያት እንደሚሞቱ የጠቆሙት በጤና ሚኒስቴር የእናቶችና ሕፃናት ጤና ዳይሬክተር ዶክተር መሠረት ዘላለም ካንሰር ስር ከሰደደ በኋላ ለማከም የሚያደርሰውን የጤና፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመቀነስና ለመከላከል ቀድሞ በመመርመር የጤናን ሁኔታ ማወቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።